ቁልፎች፡ ጄ ቀጣይ አያህ · K የቀድሞ አያህ
- 1
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ وَٱلشَّمْسِ وَضُحَىٰهَا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wash shamsi wa duhaa haa
በፀሐይና በብርሃኗ እምላለሁ፡፡
- 2
وَٱلْقَمَرِ إِذَا تَلَىٰهَا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wal qamari izaa talaa haa
በጨረቃም በተከተላት ጊዜ፤
- 3
وَٱلنَّهَارِ إِذَا جَلَّىٰهَا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wannahaari izaa jallaa haa
በቀኑም (ፀሐይን) በገለጻት ጊዜ፤
- 4
وَٱلَّيْلِ إِذَا يَغْشَىٰهَا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wallaili izaa yaghshaa haa
በሌሊቱም በሸፈናት ጊዜ፤
- 5
وَٱلسَّمَآءِ وَمَا بَنَىٰهَا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wassamaaa'i wa maa banaahaa
በሰማይቱም በገነባትም (ጌታ)፤
- 6
وَٱلْأَرْضِ وَمَا طَحَىٰهَا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wal ardi wa maa tahaahaa
በምድሪቱም በዘረጋትም፤
- 7
وَنَفْسٍۢ وَمَا سَوَّىٰهَا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa nafsinw wa maa sawwaahaa
በነፍስም ባስተካከላትም፤
- 8
فَأَلْهَمَهَا فُجُورَهَا وَتَقْوَىٰهَا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Fa-alhamahaa fujoorahaa wa taqwaahaa
አመጽዋንና ፍርሃትዋንም ባሳወቃት (አምላክ እምላለሁ)፡፡
- 9
قَدْ أَفْلَحَ مَن زَكَّىٰهَا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Qad aflaha man zakkaahaa
(ከኀጢኣት) ያጠራት ሰው ፍላጎቱን በእርግጥ አገኘ፡፡
- 10
وَقَدْ خَابَ مَن دَسَّىٰهَا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa qad khaaba man dassaahaa
(በኀጢኣት) የሸፈናትም ሰው በእውነት አፈረ፡፡
- 11
كَذَّبَتْ ثَمُودُ بِطَغْوَىٰهَآ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Kazzabat Samoodu bi taghwaahaaa
ሠሙድ ወሰን በማለፍዋ አስተባበለች፡፡
- 12
إِذِ ٱنۢبَعَثَ أَشْقَىٰهَا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Izim ba'asa ashqaahaa
ጠማማዋ በተንቀሳቀሰ ጊዜ፡፡
- 13
فَقَالَ لَهُمْ رَسُولُ ٱللَّهِ نَاقَةَ ٱللَّهِ وَسُقْيَٰهَا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Faqaala lahum Rasoolul laahi naaqatal laahi wa suqiyaahaa
ለእነርሱም የአላህ መልክተኛ (ሷሊህ) «የአላህን ግመል የመጠጥ ተራዋንም (ተጠንቀቁ)» አላቸው፡፡
- 14
فَكَذَّبُوهُ فَعَقَرُوهَا فَدَمْدَمَ عَلَيْهِمْ رَبُّهُم بِذَنۢبِهِمْ فَسَوَّىٰهَا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Fakazzaboohu fa'aqaroohaa fadamdama 'alaihim Rabbuhum bizambihim fasaw waahaa
አስተባበሉትም፡፡ (ቋንጃዋን) ወጓትም፡፡ በኀጢኣታቸውም ምክንያት ጌታቸው (ቅጣትን) በእነርሱ ላይ ደመደመባቸው፤ አስተካከላትም፡፡
- 15
وَلَا يَخَافُ عُقْبَٰهَا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa laa yakhaafu'uqbaahaa
ፍጻሜዋንም (የምታስከትለውን) አያፈራም፡፡
የትርጉም እትም፦ am.sadiq
የቁጥር ድምጽ፡ ሚሻሪ ራሺድ አላፋሲ (128kbps via islamic.network CDN)።
ጽሑፍ እና ትርጉሞች፡ api.alquran.cloud · ኡትማኒ አረብኛ።
የአያህ ትርጉም ግልጽ ካልሆነ፣ ብቁ የሆነ አስተማሪን ጠይቅ - በተለይ ለህግ እና ለእምነት ጉዳዮች።