ሁሉም ሱራዎች

ሱራ 84

The Sundering

سُورَةُ الانشِقَاقِ

Al-Inshiqaaq · መካኛ

ቁልፎች፡ ጄ ቀጣይ አያህ · K የቀድሞ አያህ

ኦዲዮ
  1. 1

    بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ إِذَا ٱلسَّمَآءُ ٱنشَقَّتْ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Izas samaaa'un shaqqat

    ሰማይ በተቀደደች ጊዜ፤

  2. 2

    وَأَذِنَتْ لِرَبِّهَا وَحُقَّتْ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa azinat li Rabbihaa wa huqqat

    ለጌታዋም (ትዕዛዝ) በሰማች ጊዜ፤ (ልትሰማ) ተገባትም፤

  3. 3

    وَإِذَا ٱلْأَرْضُ مُدَّتْ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa izal ardu muddat

    ምድርም በተለጠጠች ጊዜ፤

  4. 4

    وَأَلْقَتْ مَا فِيهَا وَتَخَلَّتْ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa alqat maa feehaa wa takhallat

    በውስጧ ያለውንም ሁሉ በጣለችና ባዶ በኾነች ጊዜ፤

  5. 5

    وَأَذِنَتْ لِرَبِّهَا وَحُقَّتْ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa azinat li Rabbihaa wa huqqat

    ለጌታዋም በሰማች ጊዜ፤ (መስማት) ተገባትም፤ (ሰው ሁሉ ሥራውን ይገናኛል)፡፡

  6. 6

    يَٰٓأَيُّهَا ٱلْإِنسَٰنُ إِنَّكَ كَادِحٌ إِلَىٰ رَبِّكَ كَدْحًۭا فَمُلَٰقِيهِ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Yaaa ayyuhal insaanu innaka kaadihun ilaa Rabbika kad han famulaaqeeh

    አንተ ሰው ሆይ! አንተ ጌታህን (በሞት) እስከምትገናኝ ድረስ ልፋትን ለፊ ነህ፤ ተገናኚውም ነህ፡፡

  7. 7

    فَأَمَّا مَنْ أُوتِىَ كِتَٰبَهُۥ بِيَمِينِهِۦ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Fa ammaa man ootiya kitaabahoo biyameenih

    መጽሐፉን በቀኙ የተሰጠ ሰውማ፤

  8. 8

    فَسَوْفَ يُحَاسَبُ حِسَابًۭا يَسِيرًۭا

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Fasawfa yuhaasabu hi saabai yaseeraa

    በእርግጥ ቀላልን ምርመራ ይመረመራል፡፡

  9. 9

    وَيَنقَلِبُ إِلَىٰٓ أَهْلِهِۦ مَسْرُورًۭا

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa yanqalibu ilaaa ahlihee masrooraa

    ወደ ቤተሰቦቹም ተደሳች ኾኖ ይመለሳል፡፡

  10. 10

    وَأَمَّا مَنْ أُوتِىَ كِتَٰبَهُۥ وَرَآءَ ظَهْرِهِۦ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa ammaa man ootiya kitaabahoo waraaa'a zahrih

    መጽሐፉን በጀርባው ኋላ የተሰጠ ሰውማ፤

  11. 11

    فَسَوْفَ يَدْعُوا۟ ثُبُورًۭا

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Fasawfa yad'oo subooraa

    (ዋ! ጥፋቴ በማለት) ጥፋትን በእርግጥ ይጠራል፡፡

  12. 12

    وَيَصْلَىٰ سَعِيرًا

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa yaslaa sa'eeraa

    የተጋጋመች እሳትንም ይገባል፡፡

  13. 13

    إِنَّهُۥ كَانَ فِىٓ أَهْلِهِۦ مَسْرُورًا

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Innahoo kaana feee ahlihee masrooraa

    እርሱ በቤተሰቡ ውስጥ ተደሳች ነበርና፡፡

  14. 14

    إِنَّهُۥ ظَنَّ أَن لَّن يَحُورَ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Innahoo zanna al lai yahoor

    እርሱ (ወደ አላህ) የማይመለስ መኾኑን አስቧልና፡፡

  15. 15

    بَلَىٰٓ إِنَّ رَبَّهُۥ كَانَ بِهِۦ بَصِيرًۭا

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Balaaa inna Rabbahoo kaana bihee baseeraa

    አይደለም (ይመለሳል)፡፡ ጌታው በእርሱ (መመለስ) ዐዋቂ ነበር፤ (ነውም)፡፡

  16. 16

    فَلَآ أُقْسِمُ بِٱلشَّفَقِ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Falaaa uqsimu bishshafaq

    አትካዱ፤ በወጋገኑ እምላለሁ፡፡

  17. 17

    وَٱلَّيْلِ وَمَا وَسَقَ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wallaili wa maa wasaq

    በሌሊቱም በሰበሰውም ሁሉ፤

  18. 18

    وَٱلْقَمَرِ إِذَا ٱتَّسَقَ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Walqamari izat tasaq

    በጨረቃውም በሞላ ጊዜ (እምላለሁ)፡፡

  19. 19

    لَتَرْكَبُنَّ طَبَقًا عَن طَبَقٍۢ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Latarkabunna tabaqan 'an tabaq

    ከኹነታ በኋላ ወደ ሌላ ኹነታ ትለዋወጣላችሁ፡፡

  20. 20

    فَمَا لَهُمْ لَا يُؤْمِنُونَ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Famaa lahum laa yu'minoon

    የማያምኑት ለእነርሱ ምን አላቸው?

  21. 21

    وَإِذَا قُرِئَ عَلَيْهِمُ ٱلْقُرْءَانُ لَا يَسْجُدُونَ ۩

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa izaa quri'a 'alaihimul Quraanu laa yasjudoon

    በእነርሱም ላይ ቁርኣን በተነበበ ጊዜ የማይሰግዱት፤ (ምንአላቸው?)

  22. 22

    بَلِ ٱلَّذِينَ كَفَرُوا۟ يُكَذِّبُونَ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Balil lazeena kafaroo yukazziboon

    በእርግጡ እነዚያ የካዱት (በትንሣኤ) ያስተባብላሉ፡፡

  23. 23

    وَٱللَّهُ أَعْلَمُ بِمَا يُوعُونَ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wallaahu a'lamu bimaa yoo'oon

    አላህም (በልቦቻቸው) የሚቆጥሩትን ዐዋቂ ነው፡፡

  24. 24

    فَبَشِّرْهُم بِعَذَابٍ أَلِيمٍ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Fabashshirhum bi'azaabin aleem

    በአሳማሚ ቅጣትም አብስራቸው፡፡

  25. 25

    إِلَّا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ وَعَمِلُوا۟ ٱلصَّٰلِحَٰتِ لَهُمْ أَجْرٌ غَيْرُ مَمْنُونٍۭ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Illal lazeena aamanoo wa 'amilus saalihaati lahum ajrun ghairu mamnoon

    ግን እነዚያ ያመኑና መልካሞችን የሠሩ ለእነርሱ የማይቆረጥ ምንዳ አልላቸው፡፡

የትርጉም እትም፦ am.sadiq

የቁጥር ድምጽ፡ ሚሻሪ ራሺድ አላፋሲ (128kbps via islamic.network CDN)።

ጽሑፍ እና ትርጉሞች፡ api.alquran.cloud · ኡትማኒ አረብኛ።

የአያህ ትርጉም ግልጽ ካልሆነ፣ ብቁ የሆነ አስተማሪን ጠይቅ - በተለይ ለህግ እና ለእምነት ጉዳዮች።