ቁልፎች፡ ጄ ቀጣይ አያህ · K የቀድሞ አያህ
- 1
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ وَيْلٌۭ لِّلْمُطَفِّفِينَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wailul lil mutaffifeen
ለሰላቢዎች ወዮላቸው፡፡
- 2
ٱلَّذِينَ إِذَا ٱكْتَالُوا۟ عَلَى ٱلنَّاسِ يَسْتَوْفُونَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Allazeena izak taaloo 'alan naasi yastawfoon
ለእነዚያ ከሰዎች ባስሰፈሩ ጊዜ የሚያስሞሉ፡፡
- 3
وَإِذَا كَالُوهُمْ أَو وَّزَنُوهُمْ يُخْسِرُونَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa izaa kaaloohum aw wazanoohum yukhsiroon
ለእነርሱም (ለሰዎቹ) በሰፈሩ ወይም በመዘኑላቸው ጊዜ የሚያጎድሉ (ለኾኑት)፡፡
- 4
أَلَا يَظُنُّ أُو۟لَٰٓئِكَ أَنَّهُم مَّبْعُوثُونَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Alaa yazunnu ulaaa'ika annahum mab'oosoon
እነዚያ እነርሱ ተቀስቃሾች መኾናቸውን አያውቁምን?
- 5
لِيَوْمٍ عَظِيمٍۢ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Li Yawmin 'Azeem
በታላቁ ቀን፡፡
- 6
يَوْمَ يَقُومُ ٱلنَّاسُ لِرَبِّ ٱلْعَٰلَمِينَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Yawma yaqoomun naasu li Rabbil 'aalameen
ሰዎች ሁሉ ለዓለማት ጌታ (ፍርድ)፤ በሚቆሙበት ቀን (ተቀስቃሾች መኾናቸውን)፡፡
- 7
كَلَّآ إِنَّ كِتَٰبَ ٱلْفُجَّارِ لَفِى سِجِّينٍۢ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Kallaaa inna kitaabal fujjaari lafee Sijjeen
በእውነት የከሓዲዎቹ (የሰላቢዎቹ) መጽሐፍ በእርግጥ በሲጂን ውስጥ ነው፡፡
- 8
وَمَآ أَدْرَىٰكَ مَا سِجِّينٌۭ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa maa adraaka maa Sijjeen
ሲጂንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?
- 9
كِتَٰبٌۭ مَّرْقُومٌۭ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Kitaabum marqoom
የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡
- 10
وَيْلٌۭ يَوْمَئِذٍۢ لِّلْمُكَذِّبِينَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wailuny yawma'izil lil mukazzibeen
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
- 11
ٱلَّذِينَ يُكَذِّبُونَ بِيَوْمِ ٱلدِّينِ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Allazeena yukazziboona bi yawmid deen
ለእነዚያ በፍርዱ ቀን ለሚያስተባብሉት፡፡
- 12
وَمَا يُكَذِّبُ بِهِۦٓ إِلَّا كُلُّ مُعْتَدٍ أَثِيمٍ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa maa yukazzibu biheee illaa kullu mu'tadin aseem
በእርሱም ወሰን አላፊ ኀጢአተኛ ሁሉ እንጅ ሌላ አያስተባብልም፡፡
- 13
إِذَا تُتْلَىٰ عَلَيْهِ ءَايَٰتُنَا قَالَ أَسَٰطِيرُ ٱلْأَوَّلِينَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Izaa tutlaa'alaihi aayaatunaa qaala asaateerul awwaleen
አንቀጾቻችን በእርሱ ላይ በተነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል፡፡
- 14
كَلَّا ۖ بَلْ ۜ رَانَ عَلَىٰ قُلُوبِهِم مَّا كَانُوا۟ يَكْسِبُونَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Kallaa bal raana 'alaa quloobihim maa kaanoo yaksiboon
ይከልከል፤ ይልቁንም በልቦቻቸው ላይ ይሠሩት የነበሩት (ኀጢአት) ደገደገባቸው፡፡
- 15
كَلَّآ إِنَّهُمْ عَن رَّبِّهِمْ يَوْمَئِذٍۢ لَّمَحْجُوبُونَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Kallaaa innahum 'ar Rabbihim yawma'izil lamah jooboon
ይከልከሉ፤ እነርሱ በዚያ ቀን ከጌታቸው (ማየት) ተጋራጆች ናቸው፡፡
- 16
ثُمَّ إِنَّهُمْ لَصَالُوا۟ ٱلْجَحِيمِ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Summa innahum lasaa lul jaheem
ከዚያም እነርሱ በእርግጥ ገሀነምን ገቢዎች ናቸው፡፡
- 17
ثُمَّ يُقَالُ هَٰذَا ٱلَّذِى كُنتُم بِهِۦ تُكَذِّبُونَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Summa yuqaalu haazal lazee kuntum bihee tukazziboon
ከዚያም «ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉበት የነበራችሁት ነው» ይባላሉ፡፡
- 18
كَلَّآ إِنَّ كِتَٰبَ ٱلْأَبْرَارِ لَفِى عِلِّيِّينَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Kallaaa inna kitaabal abraari lafee'Illiyyeen
በእውነቱ የእውነተኞቹ ምእምናን መጽሐፍ በዒሊዮን ውስጥ ነው፡፡
- 19
وَمَآ أَدْرَىٰكَ مَا عِلِّيُّونَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa maaa adraaka maa 'Illiyyoon
ዒሊዮንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?
- 20
كِتَٰبٌۭ مَّرْقُومٌۭ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Kitaabum marqoom
የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡
- 21
يَشْهَدُهُ ٱلْمُقَرَّبُونَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Yashhadu hul muqarra boon
ባለሟልዎቹ ይጣዱታል፡፡
- 22
إِنَّ ٱلْأَبْرَارَ لَفِى نَعِيمٍ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Innal abraara lafee Na'eem
እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በድሎት (ገነት) ውስጥ ናቸው፡፡
- 23
عَلَى ٱلْأَرَآئِكِ يَنظُرُونَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: 'Alal araaa'iki yanzuroon
በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው ይመለከታሉ፡፡
- 24
تَعْرِفُ فِى وُجُوهِهِمْ نَضْرَةَ ٱلنَّعِيمِ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Ta'rifu fee wujoohihim nadratan na'eem
በፊቶቻቸው ላይ የድሎትን ውበት ታውቃለህ፡፡
- 25
يُسْقَوْنَ مِن رَّحِيقٍۢ مَّخْتُومٍ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Yusqawna mir raheeqim makhtoom
ተጣርቶ ከታተመ ጠጅ ይጠጣሉ፡፡
- 26
خِتَٰمُهُۥ مِسْكٌۭ ۚ وَفِى ذَٰلِكَ فَلْيَتَنَافَسِ ٱلْمُتَنَٰفِسُونَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Khitaamuhoo misk; wa fee zaalika falyatanaafasil Mutanaafisoon
ማተሚያው ምስክ ከኾነ፤ በዚህም ተሽቀዳዳሚዎች ይሽቀዳደሙ፡፡
- 27
وَمِزَاجُهُۥ مِن تَسْنِيمٍ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa mizaajuhoo min Tasneem
መበረዣውም ከተስኒም ነው፡፡
- 28
عَيْنًۭا يَشْرَبُ بِهَا ٱلْمُقَرَّبُونَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: 'Ainaiy yashrabu bihal muqarraboon
ባለሟሎቹ ከእርሷ የሚጠጡላት ምንጭ ናት፡፡
- 29
إِنَّ ٱلَّذِينَ أَجْرَمُوا۟ كَانُوا۟ مِنَ ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ يَضْحَكُونَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Innal lazeena ajramoo kaanoo minal lazeena aamanoo yadhakoon
እነዚያ ያምመጹት በእነዚያ ባመኑት በእርግጥ ይስቁ ነበሩ፡፡
- 30
وَإِذَا مَرُّوا۟ بِهِمْ يَتَغَامَزُونَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa izaa marroo bihim yataghaamazoon
በእነርሱም ላይ ባለፉ ጊዜ ይጠቃቀሱ ነበር፡፡
- 31
وَإِذَا ٱنقَلَبُوٓا۟ إِلَىٰٓ أَهْلِهِمُ ٱنقَلَبُوا۟ فَكِهِينَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa izan qalabooo ilaaa ahlihimun qalaboo fakiheen
ወደ ቤተሰቦቻቸውም በተመለሱ ጊዜ (በመሳለቃቸው) ተደሳቾች ኾነው ይመለሱ ነበር፡፡
- 32
وَإِذَا رَأَوْهُمْ قَالُوٓا۟ إِنَّ هَٰٓؤُلَآءِ لَضَآلُّونَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa izaa ra awhum qaalooo inna haaa'ulaaa'i ladaaal loon
ባዩዋቸውም ጊዜ «እነዚህ በእርግጥ ተሳሳቾች ናቸው» ይሉ ነበር፡፡
- 33
وَمَآ أُرْسِلُوا۟ عَلَيْهِمْ حَٰفِظِينَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa maaa ursiloo 'alaihim haafizeen
በነርሱ ላይ ተጠባባቂዎች ተደርገው ያልተላኩ ሲኾኑ፡፡
- 34
فَٱلْيَوْمَ ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ مِنَ ٱلْكُفَّارِ يَضْحَكُونَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Fal yawmal lazeena aamanoo minal kuffaari yadhakoon
ዛሬ (በትንሣኤ ቀን) እነዚያ ያመኑት በከሓዲዎቹ ይስቃሉ፡፡
- 35
عَلَى ٱلْأَرَآئِكِ يَنظُرُونَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: 'Alal araaa'iki yanzuroon
በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው የሚመለከቱ ሲኾኑ (ይስቃሉ)፡፡
- 36
هَلْ ثُوِّبَ ٱلْكُفَّارُ مَا كَانُوا۟ يَفْعَلُونَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Hal suwwibal kuffaaru maa kaanoo yaf'aloon
ከሓዲዎች ይሠሩት የነበሩትን (ዋጋ) ተመነዱን? (ይላሉ)፡፡
የትርጉም እትም፦ am.sadiq
የቁጥር ድምጽ፡ ሚሻሪ ራሺድ አላፋሲ (128kbps via islamic.network CDN)።
ጽሑፍ እና ትርጉሞች፡ api.alquran.cloud · ኡትማኒ አረብኛ።
የአያህ ትርጉም ግልጽ ካልሆነ፣ ብቁ የሆነ አስተማሪን ጠይቅ - በተለይ ለህግ እና ለእምነት ጉዳዮች።