ቁልፎች፡ ጄ ቀጣይ አያህ · K የቀድሞ አያህ
- 1
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ وَٱلنَّٰزِعَٰتِ غَرْقًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wan naazi 'aati gharqa
በኃይል አውጪዎች በኾኑት፤
- 2
وَٱلنَّٰشِطَٰتِ نَشْطًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wan naa shi taati nashta
በቀስታ መምዘዝንም መዘዦች በኾኑት፤
- 3
وَٱلسَّٰبِحَٰتِ سَبْحًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wass saabi-haati sabha
መዋኘትም ዋኚዎች በኾኑት፤
- 4
فَٱلسَّٰبِقَٰتِ سَبْقًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Fass saabi qaati sabqa
መቅደምንም ቀዳሚዎች በኾኑት፤
- 5
فَٱلْمُدَبِّرَٰتِ أَمْرًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Fal mu dab-bi raati amra
ነገርንም አስተናባሪዎች በኾኑት (መላእክት) እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
- 6
يَوْمَ تَرْجُفُ ٱلرَّاجِفَةُ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Yawma tarjufur raajifa
ተርገፍጋፊይቱ (ምድር) በምትርገፈገፍበት ቀን፤
- 7
تَتْبَعُهَا ٱلرَّادِفَةُ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Tatba'u har raadifa
ለጣቂይቱ የምትከተላት ስትኾን (ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
- 8
قُلُوبٌۭ يَوْمَئِذٍۢ وَاجِفَةٌ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Quloobuny-yau maaiziw-waaji-fa
በዚያ ቀን ልቦች ተሸባሪዎች ናቸው፡፡
- 9
أَبْصَٰرُهَا خَٰشِعَةٌۭ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Absaa ruhaa khashi'ah
ዓይኖቻቸው ተዋራጆች (አቀርቃሪዎች) ናቸው፡፡
- 10
يَقُولُونَ أَءِنَّا لَمَرْدُودُونَ فِى ٱلْحَافِرَةِ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Ya qoo loona a-inna lamar doo doona fil haafirah
«እኛ ወደ መጀመሪያይቱ ኹነታ ተመላሾች ነን?» ይላሉ፡፡
- 11
أَءِذَا كُنَّا عِظَٰمًۭا نَّخِرَةًۭ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Aizaa kunna 'izaa man-nakhirah
«የበሰበሱ አጥንቶች በኾን ጊዜ (እንቀሰቀሳለን?)»
- 12
قَالُوا۟ تِلْكَ إِذًۭا كَرَّةٌ خَاسِرَةٌۭ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Qaalu tilka izan karratun khaasirah.
«ይህቺ ያን ጊዜ ባለ ከሳራ መመለስ ናት» ይላሉ፡፡
- 13
فَإِنَّمَا هِىَ زَجْرَةٌۭ وَٰحِدَةٌۭ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Fa inna ma hiya zajratuw-waahida
እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡
- 14
فَإِذَا هُم بِٱلسَّاهِرَةِ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Faizaa hum biss saahirah
ወዲያውኑም እነርሱ እንቅልፍ በሌለባት (ምድር) ላይ ይኾናሉ፡፡
- 15
هَلْ أَتَىٰكَ حَدِيثُ مُوسَىٰٓ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Hal ataaka hadeethu Musaa
የሙሳ ወሬ መጣልህን?
- 16
إِذْ نَادَىٰهُ رَبُّهُۥ بِٱلْوَادِ ٱلْمُقَدَّسِ طُوًى
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Iz nadaahu rabbuhu bil waadil-muqad dasi tuwa
ጌታው በተቀደሰው ሸለቆ በጡዋ በጠራው ጊዜ፤
- 17
ٱذْهَبْ إِلَىٰ فِرْعَوْنَ إِنَّهُۥ طَغَىٰ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Izhab ilaa fir'auna innahu taghaa.
ወደ ፈርዖን ኺድ፡፡ እርሱ ወሰን አልፏልና፡፡
- 18
فَقُلْ هَل لَّكَ إِلَىٰٓ أَن تَزَكَّىٰ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Faqul hal laka ilaa-an tazakka.
በለውም፡- «ወደ መጥራራትህ ላንተ (መንገድ) አለህን?»
- 19
وَأَهْدِيَكَ إِلَىٰ رَبِّكَ فَتَخْشَىٰ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa ahdi yaka ila rabbika fatakh sha
«ወደ ጌታህም ልመራህ ትፈራውም ዘንድ፤ (መንገድ አለህን?)» አለው፡፡
- 20
فَأَرَىٰهُ ٱلْءَايَةَ ٱلْكُبْرَىٰ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Fa araahul-aayatal kubra.
ታላቂቱንም ተዓምር አሳየው፡፡
- 21
فَكَذَّبَ وَعَصَىٰ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Fa kazzaba wa asaa.
አስተባበለም፤ አመጸም፡፡
- 22
ثُمَّ أَدْبَرَ يَسْعَىٰ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Thumma adbara yas'aa.
ከዚያም (ለማጥፋት) የሚተጋ ኾኖ ዞረ፡፡
- 23
فَحَشَرَ فَنَادَىٰ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Fa hashara fanada.
(ሰራዊቶቹን) ሰበሰበም፤ ተጣራም፡፡
- 24
فَقَالَ أَنَا۠ رَبُّكُمُ ٱلْأَعْلَىٰ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Faqala ana rabbu kumul-a'laa.
አለም፡- «እኔ ታላቁ ጌታችሁ ነኝ፡፡»
- 25
فَأَخَذَهُ ٱللَّهُ نَكَالَ ٱلْءَاخِرَةِ وَٱلْأُولَىٰٓ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Fa-akha zahul laahu nakalal aakhirati wal-oola.
አላህም በኋለኛይቱና በፊተኛይቱ (ቃል) ቅጣት ያዘው፡፡
- 26
إِنَّ فِى ذَٰلِكَ لَعِبْرَةًۭ لِّمَن يَخْشَىٰٓ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Inna fee zaalika la'ibratal limaiy-yaksha
በዚህ ውስጥ ለሚፈራ ሰው በእርግጥ መገምገሚያ አለበት፡፡
- 27
ءَأَنتُمْ أَشَدُّ خَلْقًا أَمِ ٱلسَّمَآءُ ۚ بَنَىٰهَا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: A-antum a shaddu khalqan amis samaa-u banaaha.
ባፈጣጠር እናንተ ይበልጥ የበረታችሁ ናችሁን? ወይንስ ሰማይ? (አላህ) ገነባት፡፡
- 28
رَفَعَ سَمْكَهَا فَسَوَّىٰهَا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Raf'a sam kaha fasaw waaha
ከፍታዋን አጓነ፤ አስተካከላትም፡፡
- 29
وَأَغْطَشَ لَيْلَهَا وَأَخْرَجَ ضُحَىٰهَا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa aghtasha lailaha wa akhraja duhaaha.
ሌሊቷንም አጨለመ፡፡ ቀንዋንም ገለጸ፡፡
- 30
وَٱلْأَرْضَ بَعْدَ ذَٰلِكَ دَحَىٰهَآ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wal arda b'ada zaalika dahaaha.
ምድርንም ከዚህ በኋላ ዘረጋት፡፡
- 31
أَخْرَجَ مِنْهَا مَآءَهَا وَمَرْعَىٰهَا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Akhraja minha maa-aha wa mar 'aaha.
ውሃዋንና ግጦሿን ከእርሷ አወጣ፡፡
- 32
وَٱلْجِبَالَ أَرْسَىٰهَا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wal jibala arsaaha.
ጋራዎችንም አደላደላቸው፡፡
- 33
مَتَٰعًۭا لَّكُمْ وَلِأَنْعَٰمِكُمْ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Mataa'al lakum wali an 'aamikum.
ለእናንተና ለእንስሶቻችሁ መጣቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን አደረገ)፡፡
- 34
فَإِذَا جَآءَتِ ٱلطَّآمَّةُ ٱلْكُبْرَىٰ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Fa-izaa jaaa'atit taaam matul kubraa.
ታላቂቱም መዐት በመጣች ጊዜ፣
- 35
يَوْمَ يَتَذَكَّرُ ٱلْإِنسَٰنُ مَا سَعَىٰ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Yauma Yata zakkarul insaanu ma sa'aa.
ሰው ሁሉ የሠራውን በሚያስታውስበት ቀን፣
- 36
وَبُرِّزَتِ ٱلْجَحِيمُ لِمَن يَرَىٰ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa burrizatil-jaheemu limany-yaraa.
ገሀነምም ለሚያይ ሰው በተገለጠች ጊዜ፣
- 37
فَأَمَّا مَن طَغَىٰ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Fa ammaa man taghaa.
የካደ ሰውማ፣
- 38
وَءَاثَرَ ٱلْحَيَوٰةَ ٱلدُّنْيَا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa aasaral hayaatad dunyaa
ቅርቢቱንም ሕይወት የመረጠ፣
- 39
فَإِنَّ ٱلْجَحِيمَ هِىَ ٱلْمَأْوَىٰ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Fa innal jaheema hiyal maawaa.
ገሀነም እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡
- 40
وَأَمَّا مَنْ خَافَ مَقَامَ رَبِّهِۦ وَنَهَى ٱلنَّفْسَ عَنِ ٱلْهَوَىٰ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa ammaa man khaafa maqaama Rabbihee wa nahan nafsa 'anil hawaa
በጌታው ፊት መቆምን የፈራ ሰውማ ነፍሱንም ከዝንባሌዋ የከለከለ
- 41
فَإِنَّ ٱلْجَنَّةَ هِىَ ٱلْمَأْوَىٰ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Fa innal jannata hiyal maawaa
ገነት እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡
- 42
يَسْـَٔلُونَكَ عَنِ ٱلسَّاعَةِ أَيَّانَ مُرْسَىٰهَا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Yas'aloonaka 'anis saa'ati ayyaana mursaahaa
«ከሰዓቲቱ መቼ ነው መኾኛዋ?» ሲሉ ይጠይቁሃል፡፡
- 43
فِيمَ أَنتَ مِن ذِكْرَىٰهَآ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Feema anta min zikraahaa
አንተ እርሷን ከማስታወስ በምን ውስጥ ነህ?
- 44
إِلَىٰ رَبِّكَ مُنتَهَىٰهَآ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Ilaa Rabbika muntahaa haa
(የዕውቀት) መጨረሻዋ ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
- 45
إِنَّمَآ أَنتَ مُنذِرُ مَن يَخْشَىٰهَا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Innamaaa anta munziru maiy yakshaahaa
አንተ የሚፈራትን ሰው አስፈራሪ ብቻ ነህ፡፡
- 46
كَأَنَّهُمْ يَوْمَ يَرَوْنَهَا لَمْ يَلْبَثُوٓا۟ إِلَّا عَشِيَّةً أَوْ ضُحَىٰهَا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Ka annahum Yawma yarawnahaa lam yalbasooo illaa 'ashiyyatan aw duhaahaa
እነርሱ በሚያዩዋት ቀን ያንዲት ቀን ምሽትን ወይም ረፏዷን እንጅ ያልቆዩ ይመስላሉ፡፡
የትርጉም እትም፦ am.sadiq
የቁጥር ድምጽ፡ ሚሻሪ ራሺድ አላፋሲ (128kbps via islamic.network CDN)።
ጽሑፍ እና ትርጉሞች፡ api.alquran.cloud · ኡትማኒ አረብኛ።
የአያህ ትርጉም ግልጽ ካልሆነ፣ ብቁ የሆነ አስተማሪን ጠይቅ - በተለይ ለህግ እና ለእምነት ጉዳዮች።