ቁልፎች፡ ጄ ቀጣይ አያህ · K የቀድሞ አያህ
- 1
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ عَمَّ يَتَسَآءَلُونَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: 'Amma Yatasaa-aloon
ከምን ነገር ይጠያየቃሉ?
- 2
عَنِ ٱلنَّبَإِ ٱلْعَظِيمِ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: 'Anin-nabaa-il 'azeem
ከታላቁ ዜና (ከቁርኣን ይጠያየቃሉ)፡፡
- 3
ٱلَّذِى هُمْ فِيهِ مُخْتَلِفُونَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Allazi hum feehi mukh talifoon
ከዚያ እነርሱ በእርሱ የተለያዩበት ከኾነው፡፡
- 4
كَلَّا سَيَعْلَمُونَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Kallaa sa y'alamoon
ይከልከሉ፤ ወደፊት (የሚደርስበቸውን) በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
- 5
ثُمَّ كَلَّا سَيَعْلَمُونَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Thumma kallaa sa y'alamoon
ከዚያም ይከልከሉ፤ ወደፊት ያውቃሉ፡፡
- 6
أَلَمْ نَجْعَلِ ٱلْأَرْضَ مِهَٰدًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Alam naj'alil arda mihaa da
ምድርን ምንጣፍ አላደረግንምን?
- 7
وَٱلْجِبَالَ أَوْتَادًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wal jibaala au taada
ጋራዎችንም ችካሎች አላደረግንምን?
- 8
وَخَلَقْنَٰكُمْ أَزْوَٰجًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa khalaq naakum azwaaja
ብዙ ዓይነቶችም አድርገን ፈጠርናችሁ፡፡
- 9
وَجَعَلْنَا نَوْمَكُمْ سُبَاتًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Waja'alnan naumakum subata
እንቅልፋችሁንም ዕረፍት አደረግን፡፡
- 10
وَجَعَلْنَا ٱلَّيْلَ لِبَاسًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Waja'alnal laila libasa
ሌሊቱንም ልባስ አደረግን፡፡
- 11
وَجَعَلْنَا ٱلنَّهَارَ مَعَاشًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Waja'alnan nahara ma 'aasha
ቀኑንም (ለኑሮ) መስሪያ አደረግን፡፡
- 12
وَبَنَيْنَا فَوْقَكُمْ سَبْعًۭا شِدَادًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa banaina fauqakum sab 'an shi daada
ከበላያችሁም ሰባትን ብርቱዎች (ሰማያት) ገነባን፡፡
- 13
وَجَعَلْنَا سِرَاجًۭا وَهَّاجًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Waja'alna siraajaw wah haaja
አንጸባራቂ ብርሃንንም አደረግን፡፡
- 14
وَأَنزَلْنَا مِنَ ٱلْمُعْصِرَٰتِ مَآءًۭ ثَجَّاجًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa anzalna minal m'usiraati maa-an saj-jaaja
ከአረገዙት ደመናዎችም ተንቧቢ ውሃን አወረድን፡፡
- 15
لِّنُخْرِجَ بِهِۦ حَبًّۭا وَنَبَاتًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Linukh rija bihee habbaw wana baata
በእርሱ እኽልንና ቅጠላ ቅጠልን እናወጣ ዘንድ (አወረድን)፡፡
- 16
وَجَنَّٰتٍ أَلْفَافًا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa jan naatin alfafa
የተቆላለፉ አትክልቶችንም፡፡
- 17
إِنَّ يَوْمَ ٱلْفَصْلِ كَانَ مِيقَٰتًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Inna yaumal-fasli kana miqaata
የመለያው ቀን የተወሰነ ጊዜ ነው፡፡
- 18
يَوْمَ يُنفَخُ فِى ٱلصُّورِ فَتَأْتُونَ أَفْوَاجًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Yauma yun fakhu fis-soori fataa toona afwaaja
በቀንዱ በሚነፋና የተለያዩ ጭፍሮች ኾናችሁ በምትመጡ ቀን ነው፡፡
- 19
وَفُتِحَتِ ٱلسَّمَآءُ فَكَانَتْ أَبْوَٰبًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa futiha tis samaa-u fakaanat abwaaba
ሰማይም በምትከፈትና (ባለ) ደጃፎችም በምትኾንበት፡፡
- 20
وَسُيِّرَتِ ٱلْجِبَالُ فَكَانَتْ سَرَابًا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa suyyi raatil jibaalu fa kaanat saraaba
ጋራዎችም በሚነዱበት (እንደ) ሲሪብዱም በሚኾኑበት (ቀን) ነው፡፡
- 21
إِنَّ جَهَنَّمَ كَانَتْ مِرْصَادًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Inna jahan nama kaanat mirsaada
ገሀነም መጠባበቂያ (ስፍራ) ናት፡፡
- 22
لِّلطَّٰغِينَ مَـَٔابًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Lit taa gheena ma aaba
ለሕግ ተላላፊዎች መመለሻ ስትኾን፡፡
- 23
لَّٰبِثِينَ فِيهَآ أَحْقَابًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Laa bitheena feehaa ahqaaba
በውስጧ ብዙን ዘመናት ነዋሪዎች ሲኾኑ፤
- 24
لَّا يَذُوقُونَ فِيهَا بَرْدًۭا وَلَا شَرَابًا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Laa ya zooqoona feeha bar daw walaa sharaaba
በውስጧ ቅዝቃዜንም መጠጥንም አይቀምሱም፡፡
- 25
إِلَّا حَمِيمًۭا وَغَسَّاقًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Illa hamee maw-wa ghas saaqa
ግን ሙቅ ውሃንና እዥን (ይቀምሳሉ)፡፡
- 26
جَزَآءًۭ وِفَاقًا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Jazaa-aw wi faaqa
ተስማሚን ምንዳ ይምመነዳሉ፡፡
- 27
إِنَّهُمْ كَانُوا۟ لَا يَرْجُونَ حِسَابًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Innahum kaanu laa yarjoona hisaaba
እነርሱ ምርመራን የማይፈሩ ነበሩና፡፡
- 28
وَكَذَّبُوا۟ بِـَٔايَٰتِنَا كِذَّابًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa kazzabu bi aayaa tina kizzaba
በአንቀጾቻችንም ማስተባበልን አስተባበሉና፡፡
- 29
وَكُلَّ شَىْءٍ أَحْصَيْنَٰهُ كِتَٰبًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa kulla shai-in ahsai naahu kitaa ba
ነገሩንም ሁሉ የተጻፈ ሲኾን አጠቃለልነው፡፡
- 30
فَذُوقُوا۟ فَلَن نَّزِيدَكُمْ إِلَّا عَذَابًا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Fa zooqoo falan-nazee dakum ill-laa azaaba
ቅመሱም ቅጣትንም እንጅ (ሌላን) አንጨምራችሁም (ይባላሉ)፡፡
- 31
إِنَّ لِلْمُتَّقِينَ مَفَازًا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Inna lil mutta qeena mafaaza
ለጥንቁቆቹ መዳኛ ስፍራ አልላቸው፡፡
- 32
حَدَآئِقَ وَأَعْنَٰبًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Hadaa-iqa wa a'anaa ba
አትክልቶችና ወይኖችም፡፡
- 33
وَكَوَاعِبَ أَتْرَابًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa kaawa 'iba at raaba
እኩያዎች የኾኑ ጡተ ጉቻማዎችም፡፡
- 34
وَكَأْسًۭا دِهَاقًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa ka'san di haaqa
የተሞሉ ብርጭቆዎችም፡፡
- 35
لَّا يَسْمَعُونَ فِيهَا لَغْوًۭا وَلَا كِذَّٰبًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Laa yasma'oona fiha lagh waw walaa kizzaba
በውስጧ ትርፍ ቃልንም ማስዋሸትንም አይሰሙም፡፡
- 36
جَزَآءًۭ مِّن رَّبِّكَ عَطَآءً حِسَابًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Jazaa-am mir-rabbika ataa-an hisaaba
ከጌታህ የኾነን ምንዳ በቂ ስጦታን (ተሰጡ)፡፡
- 37
رَّبِّ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلْأَرْضِ وَمَا بَيْنَهُمَا ٱلرَّحْمَٰنِ ۖ لَا يَمْلِكُونَ مِنْهُ خِطَابًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Rabbis samaa waati wal ardi wa maa baina humar rahmaani laa yam likoona minhu khi taaba
የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ሁሉ ጌታ በጣም አዛኝ ከኾነው (ተመነዱ)፡፡ ከእርሱ ጋር መነጋገርን አይችሉም፡፡
- 38
يَوْمَ يَقُومُ ٱلرُّوحُ وَٱلْمَلَٰٓئِكَةُ صَفًّۭا ۖ لَّا يَتَكَلَّمُونَ إِلَّا مَنْ أَذِنَ لَهُ ٱلرَّحْمَٰنُ وَقَالَ صَوَابًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Yauma yaqoo mur roohu wal malaa-ikatu saf-fal laa yata kalla moona illa man azina lahur rahmaanu wa qaala sawaaba
መንፈሱ (ጂብሪል) መላእክቶቹም የተሰለፉ ኾነው በሚቆሙ ቀን አል-ረሕማን ለእርሱ የፈቀደለትና ትክክለኛን ቃል ያለ ሰው ቢኾን እንጅ (መነጋገርን አይችሉም)፡፡
- 39
ذَٰلِكَ ٱلْيَوْمُ ٱلْحَقُّ ۖ فَمَن شَآءَ ٱتَّخَذَ إِلَىٰ رَبِّهِۦ مَـَٔابًا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Zaalikal yaumul haqqu faman shaa-at ta khaaza ill-laa rabbihi ma-aaba
ይህ የተረጋገጠው ቀን ነው፡፡ የሻም ሰው ወደ ጌታው መመለስን ይይዛል፡፡
- 40
إِنَّآ أَنذَرْنَٰكُمْ عَذَابًۭا قَرِيبًۭا يَوْمَ يَنظُرُ ٱلْمَرْءُ مَا قَدَّمَتْ يَدَاهُ وَيَقُولُ ٱلْكَافِرُ يَٰلَيْتَنِى كُنتُ تُرَٰبًۢا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: In naa anzar naakum azaaban qareebaiy-yauma yan zurul marr-u maa qaddamat yadaahu wa ya qoolul-kaafiru yaa lai tanee kuntu turaaba
እኛ ሰው ሁሉ እጆቹ ያስቀደሙትን በሚያይበትና ከሓዲውም ዋ ምኞቴ! ምንነው ዐፈር በኾንኩ በሚልበት ቀን ቅርብ የኾነን ቅጣት አስጠነቀቅናችሁ፡፡
የትርጉም እትም፦ am.sadiq
የቁጥር ድምጽ፡ ሚሻሪ ራሺድ አላፋሲ (128kbps via islamic.network CDN)።
ጽሑፍ እና ትርጉሞች፡ api.alquran.cloud · ኡትማኒ አረብኛ።
የአያህ ትርጉም ግልጽ ካልሆነ፣ ብቁ የሆነ አስተማሪን ጠይቅ - በተለይ ለህግ እና ለእምነት ጉዳዮች።