ቁልፎች፡ ጄ ቀጣይ አያህ · K የቀድሞ አያህ
- 1
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ وَٱلْفَجْرِ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wal-Fajr
በጎህ እምላለሁ፡፡
- 2
وَلَيَالٍ عَشْرٍۢ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa layaalin 'ashr
በዐሥር ሌሊቶችም፡፡
- 3
وَٱلشَّفْعِ وَٱلْوَتْرِ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wash shaf'i wal watr
በጥንዱም በነጠላውም፡፡
- 4
وَٱلَّيْلِ إِذَا يَسْرِ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wallaili izaa yasr
በሌሊቱም በሚኼድ ጊዜ፡፡
- 5
هَلْ فِى ذَٰلِكَ قَسَمٌۭ لِّذِى حِجْرٍ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Hal fee zaalika qasamul lizee hijr
በዚህ (መሓላ) ለባለ አእምሮ ታላቅ መሓላ አለበትን?
- 6
أَلَمْ تَرَ كَيْفَ فَعَلَ رَبُّكَ بِعَادٍ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Alam tara kaifa fa'ala rabbuka bi'aad
ጌታህ በዓድ እንዴት እንደ ሠራ አታውቅምን?
- 7
إِرَمَ ذَاتِ ٱلْعِمَادِ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Iramaa zaatil 'imaad
በኢረም በባለ ረዣዢሚቱ አዕማድ፡፡
- 8
ٱلَّتِى لَمْ يُخْلَقْ مِثْلُهَا فِى ٱلْبِلَٰدِ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Allatee lam yukhlaq misluhaa fil bilaad
በዚያች ብጤዋ በአገሮች ውስጥ ያልተፈጠረ በኾነችው፡፡
- 9
وَثَمُودَ ٱلَّذِينَ جَابُوا۟ ٱلصَّخْرَ بِٱلْوَادِ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa samoodal lazeena jaabus sakhra bil waad
በሰሙድም በእነዚያ በሸለቆው ቋጥኝን የቆረጡ በኾኑት፡፡
- 10
وَفِرْعَوْنَ ذِى ٱلْأَوْتَادِ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa fir'awna zil awtaad
በፈርዖንም ባለ ችካሎች በኾነው፡፡
- 11
ٱلَّذِينَ طَغَوْا۟ فِى ٱلْبِلَٰدِ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Allazeena taghaw fil bilaad
በእነዚያ በአገሮች ላይ ግፍ የሠሩ፡፡
- 12
فَأَكْثَرُوا۟ فِيهَا ٱلْفَسَادَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Fa aksaroo feehal fasaad
በእርሷም ውስጥ ጥፋትን ያበዙ በኾኑት (እንዴት እንደሠራ አታውቅምን?)
- 13
فَصَبَّ عَلَيْهِمْ رَبُّكَ سَوْطَ عَذَابٍ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Fasabba 'alaihim Rabbuka sawta 'azaab
በእነርሱ ላይም ጌታህ የቅጣትን አለንጋ አወረደባቸው፡፡
- 14
إِنَّ رَبَّكَ لَبِٱلْمِرْصَادِ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Inna Rabbaka labil mirsaad
ጌታህ በመጠባበቂያ ላይ ነውና፡፡
- 15
فَأَمَّا ٱلْإِنسَٰنُ إِذَا مَا ٱبْتَلَىٰهُ رَبُّهُۥ فَأَكْرَمَهُۥ وَنَعَّمَهُۥ فَيَقُولُ رَبِّىٓ أَكْرَمَنِ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Fa ammal insaanu izaa mab talaahu Rabbuhoo fa akramahoo wa na' 'amahoo fa yaqoolu Rabbeee akraman
ሰውማ ጌታው በሞከረው ጊዜ፣ ባከበረውና ባጣቀመውም (ጊዜ) «ጌታዬ አከበረኝ (አበለጠኝ)» ይላል፡፡
- 16
وَأَمَّآ إِذَا مَا ٱبْتَلَىٰهُ فَقَدَرَ عَلَيْهِ رِزْقَهُۥ فَيَقُولُ رَبِّىٓ أَهَٰنَنِ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa ammaaa izaa mabtalaahu faqadara 'alaihi rizqahoo fa yaqoolu Rabbeee ahaanan
በሞከረውና በእርሱ ላይ ሲሳዩን ባጠበበ ጊዜማ «ጌታዬ አሳነሰኝ» ይላል፡፡
- 17
كَلَّا ۖ بَل لَّا تُكْرِمُونَ ٱلْيَتِيمَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Kalla bal laa tukrimooo nal yateem
ይከልከል፤ ይልቁንም የቲምን አታከብሩም፡፡
- 18
وَلَا تَحَٰٓضُّونَ عَلَىٰ طَعَامِ ٱلْمِسْكِينِ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa laa tahaaaddoona 'alaata'aamil miskeen
ድኻንም በማብላት ላይ አትታዘዙም፡፡
- 19
وَتَأْكُلُونَ ٱلتُّرَاثَ أَكْلًۭا لَّمًّۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa taakuloonat turaasa aklal lammaa
የውርስንም ገንዘብ የመሰብሰብን አበላል ትበላላችሁ፡፡
- 20
وَتُحِبُّونَ ٱلْمَالَ حُبًّۭا جَمًّۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa tuhibboonal maala hubban jammaa
ገንዘብንም ብዙን መውደድ ትወዳላችሁ፡፡
- 21
كَلَّآ إِذَا دُكَّتِ ٱلْأَرْضُ دَكًّۭا دَكًّۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Kallaaa izaaa dukkatil ardu dakkan dakka
ተዉ፤ ምድር ደጋግማ በተሰባበረች ጊዜ፤
- 22
وَجَآءَ رَبُّكَ وَٱلْمَلَكُ صَفًّۭا صَفًّۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa jaaa'a Rabbuka wal malaku saffan saffaa
መላእክትም ሰልፍ ሰልፍ ኾነው ጌታህ (ትዕዛዙ) በመጣ ጊዜ፤
- 23
وَجِا۟ىٓءَ يَوْمَئِذٍۭ بِجَهَنَّمَ ۚ يَوْمَئِذٍۢ يَتَذَكَّرُ ٱلْإِنسَٰنُ وَأَنَّىٰ لَهُ ٱلذِّكْرَىٰ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa jeee'a yawma'izim bi jahannnam; Yawma 'iziny yatazakkarul insaanu wa annaa lahuz zikraa
ገሀነምም በዚያ ቀን በተመጣች ጊዜ በዚያ ቀን ሰው (ጥፋቱን) ይገነዘባል፡፡ መገንዘብም ለእርሱ ከየቱ?
- 24
يَقُولُ يَٰلَيْتَنِى قَدَّمْتُ لِحَيَاتِى
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Yaqoolu yaa laitanee qaddamtu lihayaatee
«ዋ እኔ! ምነው በሕይወቴ (መልካምን ሥራ) ባስቀደምኩ ኖሮ» ይላል፡፡
- 25
فَيَوْمَئِذٍۢ لَّا يُعَذِّبُ عَذَابَهُۥٓ أَحَدٌۭ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Fa Yawma izil laa yu'azzibu 'azaabahooo ahad
በዚያ ቀንም የርሱን አቀጣጥ አንድም አይቀጣም፡፡
- 26
وَلَا يُوثِقُ وَثَاقَهُۥٓ أَحَدٌۭ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa laa yoosiqu wasaaqa hooo ahad
የእርሱንም አስተሳሰር አንድም አያስርም፡፡
- 27
يَٰٓأَيَّتُهَا ٱلنَّفْسُ ٱلْمُطْمَئِنَّةُ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Yaaa ayyatuhan nafsul mutma 'innah
(ለአመነች ነፍስም) «አንቺ የረካሺው ነፍስ ሆይ!
- 28
ٱرْجِعِىٓ إِلَىٰ رَبِّكِ رَاضِيَةًۭ مَّرْضِيَّةًۭ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Irji'eee ilaa Rabbiki raadiyatam mardiyyah
«ወዳጅ ተወዳጅ ኾነሽ ወደ ጌታሽ ተመለሺ፡፡
- 29
فَٱدْخُلِى فِى عِبَٰدِى
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Fadkhulee fee 'ibaadee
«በባሮቼም ውስጥ ግቢ፡፡
- 30
وَٱدْخُلِى جَنَّتِى
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wadkhulee jannatee
ገነቴንም ግቢ፤» (ትባላለች)፡፡
የትርጉም እትም፦ am.sadiq
የቁጥር ድምጽ፡ ሚሻሪ ራሺድ አላፋሲ (128kbps via islamic.network CDN)።
ጽሑፍ እና ትርጉሞች፡ api.alquran.cloud · ኡትማኒ አረብኛ።
የአያህ ትርጉም ግልጽ ካልሆነ፣ ብቁ የሆነ አስተማሪን ጠይቅ - በተለይ ለህግ እና ለእምነት ጉዳዮች።