ሁሉም ሱራዎች

ሱራ 75

The Resurrection

سُورَةُ القِيَامَةِ

Al-Qiyaama · መካኛ

ቁልፎች፡ ጄ ቀጣይ አያህ · K የቀድሞ አያህ

ኦዲዮ
  1. 1

    بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ لَآ أُقْسِمُ بِيَوْمِ ٱلْقِيَٰمَةِ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Laaa uqsimu bi yawmil qiyaamah

    (ነገሩ ከሓዲዎች እንደሚሉት) አይደለም፡፡ በትንሣኤ ቀን እምላለሁ፡፡

  2. 2

    وَلَآ أُقْسِمُ بِٱلنَّفْسِ ٱللَّوَّامَةِ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa laaa uqsimu bin nafsil lawwaamah

    (ራሷን) ወቃሽ በኾነች ነፍስም እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡

  3. 3

    أَيَحْسَبُ ٱلْإِنسَٰنُ أَلَّن نَّجْمَعَ عِظَامَهُۥ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Ayahsabul insaanu al lan najm'a 'izaamah

    ሰው አጥንቶቹን አለመሰብሰባችንን ያስባልን?

  4. 4

    بَلَىٰ قَٰدِرِينَ عَلَىٰٓ أَن نُّسَوِّىَ بَنَانَهُۥ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Balaa qaadireena 'alaaa an nusawwiya banaanah

    አይደለም ጣቶቹን (ፊት እንደ ነበሩ) በማስተካከል ላይ ቻዮች ስንኾን (እንሰበስባቸዋለን)፡፡

  5. 5

    بَلْ يُرِيدُ ٱلْإِنسَٰنُ لِيَفْجُرَ أَمَامَهُۥ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Bal yureedul insaanu liyafjura amaamah

    ይልቁንም ሰው በፊቱ ባለው ነገር (በትንሣኤ) ሊያስተባብል ይፈልጋል፡፡

  6. 6

    يَسْـَٔلُ أَيَّانَ يَوْمُ ٱلْقِيَٰمَةِ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Yas'alu ayyyaana yawmul qiyaamah

    «የትንሣኤው ቀን መቼ ነው?» ሲል ይጠይቃል፡፡

  7. 7

    فَإِذَا بَرِقَ ٱلْبَصَرُ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Fa izaa bariqal basar

    ዓይንም በዋለለ ጊዜ፡፡

  8. 8

    وَخَسَفَ ٱلْقَمَرُ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: We khasafal qamar

    ጨረቃም በጨለመ ጊዜ፡፡

  9. 9

    وَجُمِعَ ٱلشَّمْسُ وَٱلْقَمَرُ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa jumi'ash shamusu wal qamar

    ፀሐይና ጨረቃም በተሰበሰቡ ጊዜ፡፡

  10. 10

    يَقُولُ ٱلْإِنسَٰنُ يَوْمَئِذٍ أَيْنَ ٱلْمَفَرُّ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Yaqoolul insaanu yaw ma 'izin aynal mafarr

    «ሰው በዚያ ቀን መሸሻው የት ነው?» ይላል፡፡

  11. 11

    كَلَّا لَا وَزَرَ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Kallaa laa wazar

    ይከልከል፤ ምንም መጠጊያ የለም፡፡

  12. 12

    إِلَىٰ رَبِّكَ يَوْمَئِذٍ ٱلْمُسْتَقَرُّ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Ilaa rabbika yawma 'izinil mustaqarr

    በዚያ ቀን መርጊያው ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡

  13. 13

    يُنَبَّؤُا۟ ٱلْإِنسَٰنُ يَوْمَئِذٍۭ بِمَا قَدَّمَ وَأَخَّرَ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Yunabba 'ul insaanu yawma 'izim bimaa qaddama wa akhkhar

    ሰው በዚያ ቀን ባስቀደመውና ባስቆየው ሁሉ ይነገራል፡፡

  14. 14

    بَلِ ٱلْإِنسَٰنُ عَلَىٰ نَفْسِهِۦ بَصِيرَةٌۭ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Balil insaanu 'alaa nafsihee baseerah

    በእርግጥም ሰው በነፍሱ ላይ አስረጅ ነው፡፡ (አካሎቹ ይመሰክሩበታል)፡፡

  15. 15

    وَلَوْ أَلْقَىٰ مَعَاذِيرَهُۥ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa law alqaa ma'aazeerah

    ምክንያቶቹን ሁሉ ቢያመጣም እንኳ (አይሰማም)፡፡

  16. 16

    لَا تُحَرِّكْ بِهِۦ لِسَانَكَ لِتَعْجَلَ بِهِۦٓ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Laa tuharrik bihee lisaa naka lita'jala bih

    በእርሱ (በቁርኣን ንባብ) ልትቸኩል ምላስህን በእርሱ አታላውስ፡፡

  17. 17

    إِنَّ عَلَيْنَا جَمْعَهُۥ وَقُرْءَانَهُۥ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Inna 'alainaa jam'ahoo wa qur aanah

    (በልብህ ውስጥ) መሰብሰቡና ማንበቡ በእኛ ላይ ነውና፡፡

  18. 18

    فَإِذَا قَرَأْنَٰهُ فَٱتَّبِعْ قُرْءَانَهُۥ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Fa izaa qaraanaahu fattabi' qur aanah

    ባነበብነውም ጊዜ (ካለቀ በኋላ) ንባቡን ተከተል፡፡

  19. 19

    ثُمَّ إِنَّ عَلَيْنَا بَيَانَهُۥ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Summa inna 'alainaa bayaanah

    ከዚያም ማብራራቱ በእኛ ላይ ነው፡፡

  20. 20

    كَلَّا بَلْ تُحِبُّونَ ٱلْعَاجِلَةَ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Kallaa bal tuhibboonal 'aajilah

    (ከመጣደፍ) ተከልከል፡፡ ይልቁንም (ሰዎች) ፈጣኒቱን (ዓለም) ትወዳላችሁ፡፡

  21. 21

    وَتَذَرُونَ ٱلْءَاخِرَةَ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa tazaroonal Aakhirah

    መጨረሻይቱንም (ዓለም) ትተዋላችሁ፡፡ (አትዘጋጁላትም)፡፡

  22. 22

    وُجُوهٌۭ يَوْمَئِذٍۢ نَّاضِرَةٌ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wujoohuny yawma 'izin naadirah

    ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፡፡

  23. 23

    إِلَىٰ رَبِّهَا نَاظِرَةٌۭ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Ilaa rabbihaa naazirah

    ወደ ጌታቸው ተመልካቾች ናቸው፡፡

  24. 24

    وَوُجُوهٌۭ يَوْمَئِذٍۭ بَاسِرَةٌۭ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa wujoohuny yawma 'izim baasirah

    ፊቶችም በዚያ ቀን ጨፍጋጊዎች ናቸው፡፡

  25. 25

    تَظُنُّ أَن يُفْعَلَ بِهَا فَاقِرَةٌۭ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Tazunnu any yuf'ala bihaa faaqirah

    በርሳቸውም ዐደጋ እንደሚሠራባቸው ያረጋግጣሉ፡፡

  26. 26

    كَلَّآ إِذَا بَلَغَتِ ٱلتَّرَاقِىَ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Kallaaa izaa balaghatit taraaqee

    ንቁ (ነፍስ) ብሪዎችን በደረሰች ጊዜ፤

  27. 27

    وَقِيلَ مَنْ ۜ رَاقٍۢ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa qeela man raaq

    «አሻሪው ማነው?» በተባለም ጊዜ፡፡

  28. 28

    وَظَنَّ أَنَّهُ ٱلْفِرَاقُ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa zanna annahul firaaq

    (ሕመምተኛው) እርሱ (የሰፈረበት ነገር ከዚህ ዓለም) መልለየት መኾኑን ባረጋገጠም ጊዜ፡፡

  29. 29

    وَٱلْتَفَّتِ ٱلسَّاقُ بِٱلسَّاقِ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Waltaffatis saaqu bissaaq

    ባትም በባት በተጣበቀች ጊዜ፡፡

  30. 30

    إِلَىٰ رَبِّكَ يَوْمَئِذٍ ٱلْمَسَاقُ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Ilaa rabbika yawma'izinil masaaq

    በዚያ ቀን መነዳቱ ወደ ጌታህ (ፍርድ) ነው፡፡

  31. 31

    فَلَا صَدَّقَ وَلَا صَلَّىٰ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Falaa saddaqa wa laa sallaa

    አላመነምም አልሰገደምም፡፡

  32. 32

    وَلَٰكِن كَذَّبَ وَتَوَلَّىٰ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa laakin kazzaba wa tawalla

    ግን አስተባበለ፤ (ከእምነት) ዞረም፡፡

  33. 33

    ثُمَّ ذَهَبَ إِلَىٰٓ أَهْلِهِۦ يَتَمَطَّىٰٓ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Summa zahaba ilaaa ahlihee yatamatta

    ከዚያም እየተንጎባለለ ወደ ቤተሰቡ ኼደ፡፡

  34. 34

    أَوْلَىٰ لَكَ فَأَوْلَىٰ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Awlaa laka fa awlaa

    የምትጠላውን ነገር (አላህ) ያስከትልህ፡፡ ለአንተ ተገቢህም ነው፡፡

  35. 35

    ثُمَّ أَوْلَىٰ لَكَ فَأَوْلَىٰٓ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Summa awlaa laka fa awla

    ከዚያም ጥፋት ይጠጋህ ለአንተ የተገባህም ነው፡፡

  36. 36

    أَيَحْسَبُ ٱلْإِنسَٰنُ أَن يُتْرَكَ سُدًى

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Ayahsabul insaanu anyytraka sudaa

    ሰው ስድ ኾኖ መትተውን ይጠረጥራልን?

  37. 37

    أَلَمْ يَكُ نُطْفَةًۭ مِّن مَّنِىٍّۢ يُمْنَىٰ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Alam yaku nutfatam mim maniyyiny yumnaa

    የሚፈሰስ ከኾነ የፍትወት ጠብታ አልነበረምን?

  38. 38

    ثُمَّ كَانَ عَلَقَةًۭ فَخَلَقَ فَسَوَّىٰ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Summa kaana 'alaqata fakhalaq fasawwaa

    ከዚያም የረጋ ደም ኾነ (አላህ ሰው አድርጎ) ፈጠረውም፡፡ አስተካከለውም፡፡

  39. 39

    فَجَعَلَ مِنْهُ ٱلزَّوْجَيْنِ ٱلذَّكَرَ وَٱلْأُنثَىٰٓ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Faja'ala minhuz zawjayniz zakara wal unsaa

    ከእርሱም ሁለት ዓይነቶችን ወንድና ሴትን አደረገ፡፡

  40. 40

    أَلَيْسَ ذَٰلِكَ بِقَٰدِرٍ عَلَىٰٓ أَن يُحْۦِىَ ٱلْمَوْتَىٰ

    በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Alaisa zaalika biqaadirin 'alaaa any yuhyiyal mawtaa

    ይህ (ጌታ) ሙታንን ሕያው በማድረግ ላይ ቻይ አይደለምን?

የትርጉም እትም፦ am.sadiq

የቁጥር ድምጽ፡ ሚሻሪ ራሺድ አላፋሲ (128kbps via islamic.network CDN)።

ጽሑፍ እና ትርጉሞች፡ api.alquran.cloud · ኡትማኒ አረብኛ።

የአያህ ትርጉም ግልጽ ካልሆነ፣ ብቁ የሆነ አስተማሪን ጠይቅ - በተለይ ለህግ እና ለእምነት ጉዳዮች።

The Resurrection — Islam Word