ቁልፎች፡ ጄ ቀጣይ አያህ · K የቀድሞ አያህ
- 1
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ لَآ أُقْسِمُ بِيَوْمِ ٱلْقِيَٰمَةِ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Laaa uqsimu bi yawmil qiyaamah
(ነገሩ ከሓዲዎች እንደሚሉት) አይደለም፡፡ በትንሣኤ ቀን እምላለሁ፡፡
- 2
وَلَآ أُقْسِمُ بِٱلنَّفْسِ ٱللَّوَّامَةِ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa laaa uqsimu bin nafsil lawwaamah
(ራሷን) ወቃሽ በኾነች ነፍስም እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
- 3
أَيَحْسَبُ ٱلْإِنسَٰنُ أَلَّن نَّجْمَعَ عِظَامَهُۥ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Ayahsabul insaanu al lan najm'a 'izaamah
ሰው አጥንቶቹን አለመሰብሰባችንን ያስባልን?
- 4
بَلَىٰ قَٰدِرِينَ عَلَىٰٓ أَن نُّسَوِّىَ بَنَانَهُۥ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Balaa qaadireena 'alaaa an nusawwiya banaanah
አይደለም ጣቶቹን (ፊት እንደ ነበሩ) በማስተካከል ላይ ቻዮች ስንኾን (እንሰበስባቸዋለን)፡፡
- 5
بَلْ يُرِيدُ ٱلْإِنسَٰنُ لِيَفْجُرَ أَمَامَهُۥ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Bal yureedul insaanu liyafjura amaamah
ይልቁንም ሰው በፊቱ ባለው ነገር (በትንሣኤ) ሊያስተባብል ይፈልጋል፡፡
- 6
يَسْـَٔلُ أَيَّانَ يَوْمُ ٱلْقِيَٰمَةِ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Yas'alu ayyyaana yawmul qiyaamah
«የትንሣኤው ቀን መቼ ነው?» ሲል ይጠይቃል፡፡
- 7
فَإِذَا بَرِقَ ٱلْبَصَرُ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Fa izaa bariqal basar
ዓይንም በዋለለ ጊዜ፡፡
- 8
وَخَسَفَ ٱلْقَمَرُ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: We khasafal qamar
ጨረቃም በጨለመ ጊዜ፡፡
- 9
وَجُمِعَ ٱلشَّمْسُ وَٱلْقَمَرُ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa jumi'ash shamusu wal qamar
ፀሐይና ጨረቃም በተሰበሰቡ ጊዜ፡፡
- 10
يَقُولُ ٱلْإِنسَٰنُ يَوْمَئِذٍ أَيْنَ ٱلْمَفَرُّ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Yaqoolul insaanu yaw ma 'izin aynal mafarr
«ሰው በዚያ ቀን መሸሻው የት ነው?» ይላል፡፡
- 11
كَلَّا لَا وَزَرَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Kallaa laa wazar
ይከልከል፤ ምንም መጠጊያ የለም፡፡
- 12
إِلَىٰ رَبِّكَ يَوْمَئِذٍ ٱلْمُسْتَقَرُّ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Ilaa rabbika yawma 'izinil mustaqarr
በዚያ ቀን መርጊያው ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
- 13
يُنَبَّؤُا۟ ٱلْإِنسَٰنُ يَوْمَئِذٍۭ بِمَا قَدَّمَ وَأَخَّرَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Yunabba 'ul insaanu yawma 'izim bimaa qaddama wa akhkhar
ሰው በዚያ ቀን ባስቀደመውና ባስቆየው ሁሉ ይነገራል፡፡
- 14
بَلِ ٱلْإِنسَٰنُ عَلَىٰ نَفْسِهِۦ بَصِيرَةٌۭ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Balil insaanu 'alaa nafsihee baseerah
በእርግጥም ሰው በነፍሱ ላይ አስረጅ ነው፡፡ (አካሎቹ ይመሰክሩበታል)፡፡
- 15
وَلَوْ أَلْقَىٰ مَعَاذِيرَهُۥ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa law alqaa ma'aazeerah
ምክንያቶቹን ሁሉ ቢያመጣም እንኳ (አይሰማም)፡፡
- 16
لَا تُحَرِّكْ بِهِۦ لِسَانَكَ لِتَعْجَلَ بِهِۦٓ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Laa tuharrik bihee lisaa naka lita'jala bih
በእርሱ (በቁርኣን ንባብ) ልትቸኩል ምላስህን በእርሱ አታላውስ፡፡
- 17
إِنَّ عَلَيْنَا جَمْعَهُۥ وَقُرْءَانَهُۥ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Inna 'alainaa jam'ahoo wa qur aanah
(በልብህ ውስጥ) መሰብሰቡና ማንበቡ በእኛ ላይ ነውና፡፡
- 18
فَإِذَا قَرَأْنَٰهُ فَٱتَّبِعْ قُرْءَانَهُۥ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Fa izaa qaraanaahu fattabi' qur aanah
ባነበብነውም ጊዜ (ካለቀ በኋላ) ንባቡን ተከተል፡፡
- 19
ثُمَّ إِنَّ عَلَيْنَا بَيَانَهُۥ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Summa inna 'alainaa bayaanah
ከዚያም ማብራራቱ በእኛ ላይ ነው፡፡
- 20
كَلَّا بَلْ تُحِبُّونَ ٱلْعَاجِلَةَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Kallaa bal tuhibboonal 'aajilah
(ከመጣደፍ) ተከልከል፡፡ ይልቁንም (ሰዎች) ፈጣኒቱን (ዓለም) ትወዳላችሁ፡፡
- 21
وَتَذَرُونَ ٱلْءَاخِرَةَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa tazaroonal Aakhirah
መጨረሻይቱንም (ዓለም) ትተዋላችሁ፡፡ (አትዘጋጁላትም)፡፡
- 22
وُجُوهٌۭ يَوْمَئِذٍۢ نَّاضِرَةٌ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wujoohuny yawma 'izin naadirah
ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፡፡
- 23
إِلَىٰ رَبِّهَا نَاظِرَةٌۭ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Ilaa rabbihaa naazirah
ወደ ጌታቸው ተመልካቾች ናቸው፡፡
- 24
وَوُجُوهٌۭ يَوْمَئِذٍۭ بَاسِرَةٌۭ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa wujoohuny yawma 'izim baasirah
ፊቶችም በዚያ ቀን ጨፍጋጊዎች ናቸው፡፡
- 25
تَظُنُّ أَن يُفْعَلَ بِهَا فَاقِرَةٌۭ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Tazunnu any yuf'ala bihaa faaqirah
በርሳቸውም ዐደጋ እንደሚሠራባቸው ያረጋግጣሉ፡፡
- 26
كَلَّآ إِذَا بَلَغَتِ ٱلتَّرَاقِىَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Kallaaa izaa balaghatit taraaqee
ንቁ (ነፍስ) ብሪዎችን በደረሰች ጊዜ፤
- 27
وَقِيلَ مَنْ ۜ رَاقٍۢ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa qeela man raaq
«አሻሪው ማነው?» በተባለም ጊዜ፡፡
- 28
وَظَنَّ أَنَّهُ ٱلْفِرَاقُ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa zanna annahul firaaq
(ሕመምተኛው) እርሱ (የሰፈረበት ነገር ከዚህ ዓለም) መልለየት መኾኑን ባረጋገጠም ጊዜ፡፡
- 29
وَٱلْتَفَّتِ ٱلسَّاقُ بِٱلسَّاقِ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Waltaffatis saaqu bissaaq
ባትም በባት በተጣበቀች ጊዜ፡፡
- 30
إِلَىٰ رَبِّكَ يَوْمَئِذٍ ٱلْمَسَاقُ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Ilaa rabbika yawma'izinil masaaq
በዚያ ቀን መነዳቱ ወደ ጌታህ (ፍርድ) ነው፡፡
- 31
فَلَا صَدَّقَ وَلَا صَلَّىٰ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Falaa saddaqa wa laa sallaa
አላመነምም አልሰገደምም፡፡
- 32
وَلَٰكِن كَذَّبَ وَتَوَلَّىٰ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa laakin kazzaba wa tawalla
ግን አስተባበለ፤ (ከእምነት) ዞረም፡፡
- 33
ثُمَّ ذَهَبَ إِلَىٰٓ أَهْلِهِۦ يَتَمَطَّىٰٓ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Summa zahaba ilaaa ahlihee yatamatta
ከዚያም እየተንጎባለለ ወደ ቤተሰቡ ኼደ፡፡
- 34
أَوْلَىٰ لَكَ فَأَوْلَىٰ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Awlaa laka fa awlaa
የምትጠላውን ነገር (አላህ) ያስከትልህ፡፡ ለአንተ ተገቢህም ነው፡፡
- 35
ثُمَّ أَوْلَىٰ لَكَ فَأَوْلَىٰٓ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Summa awlaa laka fa awla
ከዚያም ጥፋት ይጠጋህ ለአንተ የተገባህም ነው፡፡
- 36
أَيَحْسَبُ ٱلْإِنسَٰنُ أَن يُتْرَكَ سُدًى
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Ayahsabul insaanu anyytraka sudaa
ሰው ስድ ኾኖ መትተውን ይጠረጥራልን?
- 37
أَلَمْ يَكُ نُطْفَةًۭ مِّن مَّنِىٍّۢ يُمْنَىٰ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Alam yaku nutfatam mim maniyyiny yumnaa
የሚፈሰስ ከኾነ የፍትወት ጠብታ አልነበረምን?
- 38
ثُمَّ كَانَ عَلَقَةًۭ فَخَلَقَ فَسَوَّىٰ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Summa kaana 'alaqata fakhalaq fasawwaa
ከዚያም የረጋ ደም ኾነ (አላህ ሰው አድርጎ) ፈጠረውም፡፡ አስተካከለውም፡፡
- 39
فَجَعَلَ مِنْهُ ٱلزَّوْجَيْنِ ٱلذَّكَرَ وَٱلْأُنثَىٰٓ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Faja'ala minhuz zawjayniz zakara wal unsaa
ከእርሱም ሁለት ዓይነቶችን ወንድና ሴትን አደረገ፡፡
- 40
أَلَيْسَ ذَٰلِكَ بِقَٰدِرٍ عَلَىٰٓ أَن يُحْۦِىَ ٱلْمَوْتَىٰ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Alaisa zaalika biqaadirin 'alaaa any yuhyiyal mawtaa
ይህ (ጌታ) ሙታንን ሕያው በማድረግ ላይ ቻይ አይደለምን?
የትርጉም እትም፦ am.sadiq
የቁጥር ድምጽ፡ ሚሻሪ ራሺድ አላፋሲ (128kbps via islamic.network CDN)።
ጽሑፍ እና ትርጉሞች፡ api.alquran.cloud · ኡትማኒ አረብኛ።
የአያህ ትርጉም ግልጽ ካልሆነ፣ ብቁ የሆነ አስተማሪን ጠይቅ - በተለይ ለህግ እና ለእምነት ጉዳዮች።