ቁልፎች፡ ጄ ቀጣይ አያህ · K የቀድሞ አያህ
- 1
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ سَأَلَ سَآئِلٌۢ بِعَذَابٍۢ وَاقِعٍۢ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Sa ala saaa'ilum bi'azaa binw-waaqi'
ወዳቂ ከኾነው ቅጣት ጠያቂ ጠየቀ፡፡
- 2
لِّلْكَٰفِرِينَ لَيْسَ لَهُۥ دَافِعٌۭ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Lilkaafireen laisa lahoo daafi'
በከሓዲዎች ላይ (ወዳቂ ከኾነው) ለእርሱ መላሽ የለውም፡፡
- 3
مِّنَ ٱللَّهِ ذِى ٱلْمَعَارِجِ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Minal laahi zil ma'aarij
የ(ሰማያት) መሰላሎች ባለቤት ከኾነው አላህ (መላሽ የለውም)፡፡
- 4
تَعْرُجُ ٱلْمَلَٰٓئِكَةُ وَٱلرُّوحُ إِلَيْهِ فِى يَوْمٍۢ كَانَ مِقْدَارُهُۥ خَمْسِينَ أَلْفَ سَنَةٍۢ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Ta'rujul malaaa'ikatu war Roohu ilaihi fee yawmin kaana miqdaaruhoo khamseena alfa sanah
መላእክቱና መንፈሱም ልኩ አምሳ ሺሕ ዓመት በኾነ ቀን ውስጥ ወደእርሱ ያርጋሉ፤ (ይወጣሉ)፡፡
- 5
فَٱصْبِرْ صَبْرًۭا جَمِيلًا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Fasbir ssabran jameelaa
መልካምንም ትዕግስት ታገሥ፡፡
- 6
إِنَّهُمْ يَرَوْنَهُۥ بَعِيدًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Inaahum yarawnahoo ba'eedaa
እነርሱ (ያንን ቀን) ሩቅ አድርገው ያዩታል፡፡
- 7
وَنَرَىٰهُ قَرِيبًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa naraahu qareebaa
እኛም ቅርብ ኾኖ እናየዋለን፡፡
- 8
يَوْمَ تَكُونُ ٱلسَّمَآءُ كَٱلْمُهْلِ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Yawma takoonus samaaa'u kalmuhl
ሰማይ እንደ ዘይት አተላ በምትኾንበት ቀን፡፡
- 9
وَتَكُونُ ٱلْجِبَالُ كَٱلْعِهْنِ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa takoonul jibaalu kal'ihn
ጋራዎችም በተለያዩ ቀለማት እንደ ተነከረ ሱፍ (ነፋስ እንደሚያበረው) በሚኾኑበት ቀን፡፡
- 10
وَلَا يَسْـَٔلُ حَمِيمٌ حَمِيمًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa laa yas'alu hameemun hameemaa
ዘመድም ዘመድን በማይጠይቅበት ቀን፤ (መላሽ የለውም)፡፡
- 11
يُبَصَّرُونَهُمْ ۚ يَوَدُّ ٱلْمُجْرِمُ لَوْ يَفْتَدِى مِنْ عَذَابِ يَوْمِئِذٍۭ بِبَنِيهِ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Yubassaroonahum; ya waddul mujrimu law yaftadee min 'azaabi yawma'izim bibaneeh
(ዘመዶቻቸውን) ያዩዋቸዋል፡፡ አመጸኛው ከዚያ ቀን ስቃይ (ነፍሱን) በልጆቹ ሊበዥ ይመኛል፡፡
- 12
وَصَٰحِبَتِهِۦ وَأَخِيهِ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa saahibatihee wa akheeh
በሚስቱም በወንድሙም፡፡
- 13
وَفَصِيلَتِهِ ٱلَّتِى تُـْٔوِيهِ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa faseelathil latee tu'weeh
በዚያችም በምታስጠጋው ጎሳው፡፡
- 14
وَمَن فِى ٱلْأَرْضِ جَمِيعًۭا ثُمَّ يُنجِيهِ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa man fil ardi jamee'an summa yunjeeh
በምድርም ላይ ባለው ሁሉ (ሊበዥ) ከዚያም ሊያድነው (ይመኛል)፡፡
- 15
كَلَّآ ۖ إِنَّهَا لَظَىٰ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Kallaa innahaa lazaa
ይተው! እርሷ (እሳቲቱ) ለዟ ናት፡፡
- 16
نَزَّاعَةًۭ لِّلشَّوَىٰ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Nazzaa'atal lishshawaa
የራስን ቅል ቆዳ የምትሞሽልቅ ስትኾን፡፡
- 17
تَدْعُوا۟ مَنْ أَدْبَرَ وَتَوَلَّىٰ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Tad'oo man adbara wa tawallaa
(ከእምነት) የዞረንና የሸሸን ሰው (ወደእርሷ) ትጠራለች፡፡
- 18
وَجَمَعَ فَأَوْعَىٰٓ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: W jama'a fa aw'aa
ገንዘብን የሰበሰበንና (ዘካውን ሳይሰጥ) የቆጠረንም፤ (ትጠራለች)፡፡
- 19
۞ إِنَّ ٱلْإِنسَٰنَ خُلِقَ هَلُوعًا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Innal insaana khuliqa haloo'aa
ሰው ቅጠ ቢስ ኾኖ ተፈጠረ፡፡
- 20
إِذَا مَسَّهُ ٱلشَّرُّ جَزُوعًۭا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Izaa massahush sharru jazoo'aa
ክፉ ነገር ባገኘው ጊዜ ብስጪተኛ፡፡
- 21
وَإِذَا مَسَّهُ ٱلْخَيْرُ مَنُوعًا
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wa izaa massahul khairu manoo'aa
መልካምም ነገር (ድሎት) ባገኘ ጊዜ ከልካይ (ኾኖ ተፈጠረ)፡፡
- 22
إِلَّا ٱلْمُصَلِّينَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Illal musalleen
ሰጋጆቹ ብቻ ሲቀሩ፡፡
- 23
ٱلَّذِينَ هُمْ عَلَىٰ صَلَاتِهِمْ دَآئِمُونَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Allazeena hum 'alaa Salaatihim daaa'imoon
እነዚያ እነርሱ በስግደታቸው ላይ ዘውታሪዎች የኾኑት፡፡
- 24
وَٱلَّذِينَ فِىٓ أَمْوَٰلِهِمْ حَقٌّۭ مَّعْلُومٌۭ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wallazeena feee amwaalihim haqqum ma'loom
እነዚያም በገንዘቦቻቸው ላይ የታወቀ መብት ያለባቸው የኾኑት፡፡
- 25
لِّلسَّآئِلِ وَٱلْمَحْرُومِ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Lissaaa 'ili walmahroom
ለለማኝ ከልመና ለሚከለከልም (መብት ያለባቸው የኾኑት)፡፡
- 26
وَٱلَّذِينَ يُصَدِّقُونَ بِيَوْمِ ٱلدِّينِ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wallazeena yusaddiqoona bi yawmid Deen
እነዚያም በፍርዱ ቀን እውነት የሚሉት (የሚያረጋግጡት)፡፡
- 27
وَٱلَّذِينَ هُم مِّنْ عَذَابِ رَبِّهِم مُّشْفِقُونَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wallazeena hum min 'azaabi Rabbihim mushfiqoon
እነዚያም እነርሱ ከጌታቸው ቅጣት ፈሪዎች የኾኑት፡፡
- 28
إِنَّ عَذَابَ رَبِّهِمْ غَيْرُ مَأْمُونٍۢ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Inna 'azaaba Rabbihim ghairu maamoon
የጌታቸው ቅጣት (መምጣቱ) የማያስተማምን ነውና፡፡
- 29
وَٱلَّذِينَ هُمْ لِفُرُوجِهِمْ حَٰفِظُونَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wallazeena hum lifuroo jihim haafizoon
እነዚያም እነርሱ ብልቶቻቸውን ጠባቂዎች የኾኑት፡፡
- 30
إِلَّا عَلَىٰٓ أَزْوَٰجِهِمْ أَوْ مَا مَلَكَتْ أَيْمَٰنُهُمْ فَإِنَّهُمْ غَيْرُ مَلُومِينَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Illaa 'alaaa azwaajihim aw maa malakat aymaanuhum fainnahum ghairu maloomeen
በሚስቶቻቸው ወይም እጆቻቸው በያዙዋቸው (ባሪያዎች) ላይ ሲቀር፡፡ እነርሱ (በእነዚህ) የማይወቀሱ ናቸውና፡፡
- 31
فَمَنِ ٱبْتَغَىٰ وَرَآءَ ذَٰلِكَ فَأُو۟لَٰٓئِكَ هُمُ ٱلْعَادُونَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Famanib taghaa waraaa'a zaalika fa ulaaa'ika humul 'aadoon
ከዚያም ወዲያ የፈለገ ሰው እነዚያ እነሱ ድንበር አላፊዎች ናቸው፡፡
- 32
وَٱلَّذِينَ هُمْ لِأَمَٰنَٰتِهِمْ وَعَهْدِهِمْ رَٰعُونَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wallazeena hum li amaa naatihim wa 'ahdihim raa'oon
እነዚያም እነርሱ አደራዎቻቸውንና ቃል ኪዳናቸውን ጠባቂዎች የኾኑት፡፡
- 33
وَٱلَّذِينَ هُم بِشَهَٰدَٰتِهِمْ قَآئِمُونَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wallazeena hum bishahaadaatihim qaaa'imoon
እነዚያም እነርሱ በምስክርነታቸው ትክክለኞች የኾኑት፡፡
- 34
وَٱلَّذِينَ هُمْ عَلَىٰ صَلَاتِهِمْ يُحَافِظُونَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Wallazeena hum 'alaa salaatihim yuhaafizoon
እነዚያም እነርሱ በሶላቶቻቸው ላይ የሚጠባበቁት፡፡
- 35
أُو۟لَٰٓئِكَ فِى جَنَّٰتٍۢ مُّكْرَمُونَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Ulaaa'ika fee jannaatim mukramoon
እነዚህ (ከዚህ በላይ የተወሱት ሁሉ) በገነቶች ውስጥ የሚከበሩ ናቸው፡፡
- 36
فَمَالِ ٱلَّذِينَ كَفَرُوا۟ قِبَلَكَ مُهْطِعِينَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Famaa lil lazeena kafaroo qibalaka muhti'een
ለእነዚያም ለካዱት ወደ አንተ በኩል አንገቶቻቸውን መዝዘው የሚያተኩሩት ምን አላቸው?
- 37
عَنِ ٱلْيَمِينِ وَعَنِ ٱلشِّمَالِ عِزِينَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: 'Anil yameeni wa 'anish shimaali 'izeen
ከቀኝና ከግራ ክፍልፍል ጭፍሮች ሲኾኑ፡፡
- 38
أَيَطْمَعُ كُلُّ ٱمْرِئٍۢ مِّنْهُمْ أَن يُدْخَلَ جَنَّةَ نَعِيمٍۢ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Ayatma'u kullum ri'im minhum anyyudkhala jannata Na'eem
ከእነርሱ እያንዳንዱ ሰው የጸጋይቱን ገነት መግባትን ይከጅላልን?
- 39
كَلَّآ ۖ إِنَّا خَلَقْنَٰهُم مِّمَّا يَعْلَمُونَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Kallaaa innaa khalaq nahum mimmaa ya'lamoon
ይከልከል፤ እኛ ከሚያውቁት ነገር (ከፍቶት ጠብታ) ፈጠርናቸው፡፡
- 40
فَلَآ أُقْسِمُ بِرَبِّ ٱلْمَشَٰرِقِ وَٱلْمَغَٰرِبِ إِنَّا لَقَٰدِرُونَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Falaaa uqsimu bi Rabbil mashaariqi wal maghaaribi innaa laqaadiroon
በምሥራቆችና በምዕራቦችም ጌታ እምላለሁ፡፡ እኛ በእርግጥ ቻዮች ነን፡፡
- 41
عَلَىٰٓ أَن نُّبَدِّلَ خَيْرًۭا مِّنْهُمْ وَمَا نَحْنُ بِمَسْبُوقِينَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: 'Alaaa an nubaddila khairam minhum wa maa Nahnu bimasbooqeen
ከእነርሱ የተሻለን በመለወጥ ላይ፡፡ እኛም ተሸናፊዎች አይደለንም፡፡
- 42
فَذَرْهُمْ يَخُوضُوا۟ وَيَلْعَبُوا۟ حَتَّىٰ يُلَٰقُوا۟ يَوْمَهُمُ ٱلَّذِى يُوعَدُونَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Fazarhum yakhoodoo wa yal'aboo hattaa yulaaqoo yaw mahumul lazee yoo'adoon
ያንንም የሚስፈራሩበትን ቀናቸውን እስከሚገናኙ ድረስ ተዋቸው፡፡ ይዋኙ ይጫወቱም፡፡
- 43
يَوْمَ يَخْرُجُونَ مِنَ ٱلْأَجْدَاثِ سِرَاعًۭا كَأَنَّهُمْ إِلَىٰ نُصُبٍۢ يُوفِضُونَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Yawma yakhrujoona minal ajdaasi siraa'an ka anna hum ilaa nusubiny yoofidoon
ወደ ጣዖቶች እንደሚሽቀዳደሙ ኾነው ከመቃብሮቻቸው ፈጥነው የሚወጡበትን ቀን (እስከሚገናኙ ድረስ ተዋቸው)፡፡
- 44
خَٰشِعَةً أَبْصَٰرُهُمْ تَرْهَقُهُمْ ذِلَّةٌۭ ۚ ذَٰلِكَ ٱلْيَوْمُ ٱلَّذِى كَانُوا۟ يُوعَدُونَ
በቋንቋ ፊደል መጻፍ: Khaashi'atan absaaruhum tarhaquhum zillah; zaalikal yawmul lazee kaanoo yoo'adoon
ዓይኖቻቸው ያፈሩ ኾነው ውርደት ትሸፍናቸዋለች፡፡ ይህ ቀን ያ ይስፈራሩበት የነበሩት ነው፡፡
የትርጉም እትም፦ am.sadiq
የቁጥር ድምጽ፡ ሚሻሪ ራሺድ አላፋሲ (128kbps via islamic.network CDN)።
ጽሑፍ እና ትርጉሞች፡ api.alquran.cloud · ኡትማኒ አረብኛ።
የአያህ ትርጉም ግልጽ ካልሆነ፣ ብቁ የሆነ አስተማሪን ጠይቅ - በተለይ ለህግ እና ለእምነት ጉዳዮች።